Text copied!
Bibles in Amharic

የዮሐንስ ወንጌል 7:46-52 in Amharic

Help us?

የዮሐንስ ወንጌል 7:46-52 in መጽሐፍ ቅዱስ

46 ሎሌዎቹ። እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም ብለው መለሱ።
47 እንግዲህ ፈሪሳውያን። እናንተ ደግሞ ሳታችሁን?
48 ከአለቆች ወይስ ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለን?
49 ነገር ግን ሕግን የማያውቀው ይህ ሕዝብ ርጉም ነው ብለው መለሱላቸው።
50 ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ።
51 ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።
52 እነርሱም መለሱና። አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ ከገሊላ እንዳይነሣ መርምርና እይ አሉት።
የዮሐንስ ወንጌል 7 in መጽሐፍ ቅዱስ