Text copied!
Bibles in Amharic

የዮሐንስ ወንጌል 6:16-21 in Amharic

Help us?

የዮሐንስ ወንጌል 6:16-21 in መጽሐፍ ቅዱስ

16 በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ባሕር ወረዱ፥
17 በታንኳም ገብተው በባሕር ማዶ ወደ ቅፍርናሆም ይመጡ ነበር። አሁንም ጨልሞ ነበር፤ ኢየሱስም ገና ወደ እነርሱ አልመጣም ነበር፤
18 ብርቱ ነፋስም ስለ ነፈሰ ባሕሩ ተናወጠ።
19 ሀያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ከቀዘፉ በኋላም፥ ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ታንኳይቱ ሲቀርብ አይተው ፈሩ።
20 እርሱ ግን። እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
21 ስለዚህ በታንኳይቱ ሊቀበሉት ወደዱ፤ ወዲያውም ታንኳይቱ ወደሚሄዱበት ምድር ደረሰች።
የዮሐንስ ወንጌል 6 in መጽሐፍ ቅዱስ